Subscribers
4.0K
Current member count
Type
Channel
Telegram channel
Global Rank
#421
Directory ranking
Live Channel Feed
View on Telegram
በመዲናዋ በትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ
በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ በዛሬው ዕለት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡
በክፍለ ከተማው ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን አካባቢ በደረሰው አደጋ ከሟቾች በተጨማሪ ሌሎች ሰዎችም ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው የከተማው ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል፡፡፡
ዛሬ ጠዋት 1 ሰዓት ከ50 ከኮዬ ፈቼ ወደ ጎሮ በመጓዝ ላይ የነበረ ሚኒባስ ተሽከርካሪ በተጠቀሰው አካባቢ በመንገድ ስራ ላይ የነበረ ስካቫተር ማሽን መቆፈሪያው ወድቆበት በታክሲው ውስጥ ከነበሩ ትራንስፖርት ተጠቃሚዎች መካከል የ6ቱ ህይወት አልፏል፡፡
ከሟቾች በተጨማሪ በታክሲ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና ክትትል በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑንም ፖሊስ አስታውቋል፡፡
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
-ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_merejaበመዲናዋ በትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ
በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ በዛሬው ዕለት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡
በክፍለ ከተማው ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን አካባቢ በደረሰው አደጋ ከሟቾች በተጨማሪ ሌሎች ሰዎችም ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው የከተማው ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል፡፡፡
ዛሬ ጠዋት 1 ሰዓት ከ50 ከኮዬ ፈቼ ወደ ጎሮ በመጓዝ ላይ የነበረ ሚኒባስ ተሽከርካሪ በተጠቀሰው አካባቢ በመንገድ ስራ ላይ የነበረ ስካቫተር ማሽን መቆፈሪያው ወድቆበት በታክሲው ውስጥ ከነበሩ ትራንስፖርት ተጠቃሚዎች መካከል የ6ቱ ህይወት አልፏል፡፡
ከሟቾች በተጨማሪ በታክሲ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና ክትትል በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑንም ፖሊስ አስታውቋል፡፡
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
-ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_mereja
Aug 24, 08:27 AM
7.38K

የተማሪዎች ውጤት መቼ ይለቀቃል?
ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት ይችላሉ።
በውጤታቸው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ከሆነም 5/6 ቀናት ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ" ዘንድሮ ካለፉት ዓመታት ውጤት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ተማሪ ቁጥር ያለፈ በመሆኑ የምንቀበለው የሬሚዲያል ተማሪ ቁጥር ይቀንሳል። ስንት ይሆናል የሚለውን በተመለከተ ግን መቁረጫ ነጥቡ ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል። " ብለዋል።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
-ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_merejaየተማሪዎች ውጤት መቼ ይለቀቃል?
ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት ይችላሉ።
በውጤታቸው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ከሆነም 5/6 ቀናት ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ" ዘንድሮ ካለፉት ዓመታት ውጤት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ተማሪ ቁጥር ያለፈ በመሆኑ የምንቀበለው የሬሚዲያል ተማሪ ቁጥር ይቀንሳል። ስንት ይሆናል የሚለውን በተመለከተ ግን መቁረጫ ነጥቡ ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል። " ብለዋል።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
-ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_mereja
Aug 22, 03:37 PM
11.9K

#NationalExam
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ስለ 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መግለጫ እየሰጡ ነው።
በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 563 ሺ 960 ተማሪዎች ተመዝግበው 550 ሺ 210 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል።
ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 12.8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ችለዋል።
ዘንድሮ በአጠቃላይ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ማለፍ የቻሉት 70 ሺ 544 ናቸው።
ካለፉት መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ ሲሆኑ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
-ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_mereja#NationalExam
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ስለ 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መግለጫ እየሰጡ ነው።
በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 563 ሺ 960 ተማሪዎች ተመዝግበው 550 ሺ 210 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል።
ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 12.8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ችለዋል።
ዘንድሮ በአጠቃላይ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ማለፍ የቻሉት 70 ሺ 544 ናቸው።
ካለፉት መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ ሲሆኑ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
-ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_mereja
Aug 22, 02:34 PM
11.6K

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በዕጩነት ያቀረባቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሹመት በብሔራዊ ባንክ ውድቅ ሆነ
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የቀድሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚውን እንዲተኩ በተጠባባቂነት የሰየማቸውን ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ውድቅ ማድረጉ ተሰማ፡፡
በግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ውስጥ ተፈጥሮ በነበረው ችግር ሳቢያ የባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ ዋና ሥራ አስፈጻሚውን ጨምሮ 18 የባንኩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ከኃላፊነታቸው ማንሳቱና ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክም የባንኩን የቀድሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለአምስት ዓመት በየትኛውም የፋይናንስ ተቋማት እንዳያገለግሉ እንዳገደ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
ይህንን ውሳኔ ተከትሎ የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ቦርድ አዲስ ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሰየም ሹመቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንዲያፀድቅለት ቢልክም፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሹመቱን ሳያፀድቅ ቀርቷል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚውን ሹመት ያልተቀበለውና ሹመቱንም የማያፀድቅ መሆኑን ለግሎባል ኢትዮጵያ ባንክ ቦርድ በጽሑፍ ማሳወቁንም ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ብሔራዊ ባንክ ሹመቱን ያላፀደቀበትን ምክንያት በደብዳቤው ማሳወቁ የተመለከተ ሲሆን፣ በዋናነት የጠቀሰው ምክንያትም በባንክ ሥራ አዋጅ አንድ የባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሊያሟላ ይገባል ተብሎ የተዘረዘሩትን መሥፈርቶች ለዋና ሥራ አስፈጻሚነት የታጩት ግለሰብ አያሟሉም የሚል ነው፡፡ ባንኩ ለዋና ሥራ አስፈጻሚነት ያጫቸው አቶ ሳህለ ሚካኤል መኮንን መሆናቸውን ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
-ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_mereja
Aug 21, 11:38 AM
13.4K

በአቶ ታዬ ደንደአ ላይ ተጥሎ የነበረው የአራት ዓመት የጽኑ እስራት ውሳኔ በሰበር ሰሚ ችሎት ጸደቀ
#Ethiopia | የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የቀድሞው የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ አቶ ታዬ ደንደአ ላይ የታዘዘውን የአራት ዓመታት የእስር ቅጣት ሙሉ በሙሉ ማጸናቱን አስታወቀ።
ችሎቱ በአዲስ አበባ በዋለው ሰበር ችሎት በአቶ ታዬ ደንደአ በኩል የቀረበውን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ በታችኛው ፍርድ ቤት ተበይኖ የነበረውን ውሳኔ አጽንቶታል።
አቶ ታዬ በመጀመሪያ ደረጃ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት በሚል በተመሠረተባቸው ክስ የሰባት ዓመት እስር ተፈርዶባቸው የነበረ ቢሆንም ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረቡት ይግባኝ ቅጣቱ ወደ አራት ዓመት ዝቅ እንዲል ተደርጎ ነበር።
ይሁን እንጂ በተሰጠው ውሳኔ ላይ ቅሬታ የነበራቸው አቶ ታዬ አምስት የመከራከሪያ ነጥቦችን በማንሳት ለፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት አቤቱታቸውን ቢያቀርቡም ችሎቱ የቀረበውን ጥያቄ ሳይቀበለው ቀርቷል።
የአቶ ታዬ ደንደአ ባለቤት ወይዘሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ ለዶቼ ቬለ በሰጡት ቃል ባለቤታቸው የመሣሪያውን መገኘት ባያስተባብሉም ከሌሎች ዜጎች እኩል የመዳኘት መብት እንደተከለከሉ እና ካቀረቧቸው አምስት ተከላካይ ምስክሮች መካከል የሁለቱ ብቻ ቃል ተሰምቶ ውሳኔ መሰጠቱን በቅሬታነት ማቅረባቸውን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል አቃቤ ሕግ ይግባኝ ባሰማበት ተጓዳኝ የክስ ነጥብ ላይ ፍርድ ቤቱ ለጥቅምት 17 ቀን 2019 ዓ.ም. ቀጣይ ቀጠሮ ሰጥቷል።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
-ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_mereja
Aug 20, 09:07 PM
14.2K
Safety & Compliance Disclaimer
TelePilot Pro is not affiliated with Telegram. Listings are based on publicly available community information. We index public groups, channels, and bots only. No private user data, phone numbers, or locked session files are stored or displayed.
TelePilot Pro Automation
Scale Your Telegram Community Faster
Join thousands of marketers using TelePilot Pro to bulk message, scrape targeted members, and manage groups on autopilot. Outperform competitors with our 40+ professional automation tools.
